top of page

አቢጋኤል ዮሐንስ ፋውንዴሽን

አቢጋኤል ለመጻሕፍት ልዩ ፍቅር የነበራት ወጣት ነበረች። መጻሕፍትን ብቻ አታነብም ነበር፤ በውስጣቸው ያሉ ታሪኮችን፣ ስሜቶችን እና ሀሳቦችን በጥልቀት ትረዳ ነበር።

መጻሕፍት የተለያዩ ሰዎችን ታሪክ እንደታውቅ፣ ባህሎችን እና የሕይወት ተሞክሮዎችን እንድትረዳ ይረዷት ነበር። እንደ ጥሩ የመጽሐፍ ገምጋሚ፣ ያነበበችውን መጽሐፍ ሀሳብ፣ እና የተረዳችውን ቁምነገር  ለሌሎች ማካፈል ትወድ ነበር።

አቢጋይል ከወላጆቿና ከጓደኞቿ ጋር ስለ መጻሕፍት መወያየት፣ የወደደችውን ታሪክ ማስረዳት እና ያገኘችውን ትምህርት ማካፈል ትወድ ነበር።

አቢጋይል የራሷን ጽሑፎች ትጽፍ ነበር። ሀሳቦቿን፣ ስሜቶቿን እና የፈጠራ ችሎታዋን በጽሑፍ ማሳየት ትወድ ነበር።

ከምትወዳቸው ደራሲዎች መካከል Toni Morrison አንዷ ነበረች። አቢጋይል ጥልቅ ትርጉም ያላቸው ታሪኮችን እና የሰዎችን ሕይወትና ስሜት በቃላት የማሳየት ችሎታን ታደንቅ ነበር።

እንዲሁም ግጥምን በጣም ትወድ ነበር። ግጥም ስሜትን፣ ምናብን እና የቃላትን ውበት ለመግለጽ መንገድ ነበር ብላ ታምናለች።

የአቢጋኤል የመጽሐፍ ማዕድ

ወደ አቢጋይል የመጽሐፍ ማዕድ እንኳን በደህና መጡ።

ይህ ቦታ የንባብ፣ የታሪክ እና የፈጠራ ፍቅርን ለማካፈል የተዘጋጀ ነው።

እርስዎም፦

  •  የሚወዱትን መጽሐፍ ግምገማ ማጋራት ይችላሉ

  •  አጭር ታሪክ ወይም ግጥም መጻፍ ይችላሉ

  •  ከመጽሐፍ ያገኙትን ትምህርት ማካፈል ይችላሉ

  •  ያነበቡትነ መጽሀፍ  መጠቆም ይችላሉ

  • ለአቢጋይል መታሰቢያ ጽሑፍዎን ማካፈል ይችላሉ 

የፋውንዴሽኑ ዋና አላማዎች፡

  • ቤተ-መጻሕፍትን መገንባት እና መጻሕፍትን ማሰራጨት፡ መጻሕፍት ለሁሉም ህፃናትና ወጣቶች ተደራሽ እንዲሆኑ ማድረግ።

  • የንባብ ባህልን ማጎልበት፡ 

  • አዳዲስ ድምፆችን ማበረታታት፡ ፅሁፍ እና ጥበብ ላይ ትኩረት የሚያደርጉ መድረኮችን በማዘጋጀት ታታሪ ወጣት ፀሀፊያንን መደገፍ።

 

እያንዳንዱ ልጅ መጻሕፍትን የማግኘት፣ የማለም፣ የመማር እና የማደግ እድል ይገባዋል ብለን እንምናምናለን። የአቢጌይልን የስነ-ጽሁፍ ፍቅር በማስቀጠል፣ መጪው ትውልድ የንባብን ሀይል እና የእውቀትን ውበት እንዲያገኝ ማነሳሳት የዘወትር ተግባራችን ነው።

IMG_2344.jpeg
መንገድ ስጡኝ ስፊ / ገብረ ክርስቶስ ደስታ
IMG_2755.PNG
IMG_2758.jpg
IMG_2787.PNG
IMG_2792.PNG
bottom of page